ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

ደንበኛ ተኮር ስርዓት የወለደው የነዋሪዎች አንድነት ከድርጅቱ አልፎ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋርም እያስተሳሰረ መሆኑ ተገለጸ

ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. #ኢኦተቤክ_ቤሕአልድ አዲስአበባ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የተጀመረው ደንበኛ ተኮር ስርዓት ደንበኞችን ከድርጅቱ ጋር ከማቆራኘት አልፎ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጋር መናበብን የፈጠረ ሲሆን ይህንኑ በሚገልጽና ተባባሪነትን በሚያሳይ መልኩ በዛሬው እለት የጽዳት ዘመቻ አካሂዷል። የጽዳት ዘመቻው ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ […]

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የፈነጠቀው የልማት ጀምበር ለሁሉም መዳረስ እንደሚገባው ተጠቆመ

ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ_ቤሕአልድ አዲስአበባ ኢትዮጵያ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ የሚመራው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ለስብከተ ወንጌል፣ ለልማት፣ለቴክኖሎጂና ለሚዲያ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት አንቱታን ያተረፈ ሲሆን በ2018ዓ.ም በጀት ዓመት በርካታ […]

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊ በመሆኗ አበው ቅዱሳን በፍትሕ መንፈሳዊና በጉባኤ አድያም ዘአንጾኪያ “ወይኩን ሲኖዶስ ዘጳጳሳት ፪ተ ጊዜያተ በበዓመት – የጳጳሳት ጉባኤም በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን” […]

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን! ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅ፤ ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፤ ብፁዕ ኣቡነ ሕርያቆስ የኣዲስ ኣበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት፣ በኣጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፦ ማሕየዊት በምትሆን ሞቱ ሰማያውያንና […]

ለዘመናት የቤተክርስቲያንን ተልእኮ በማሳለጥ የሚታወቀው የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በበጀት ዓመቱ ለሦስተኛ ጊዜ ዐቢይ ጉባኤ አካሄደ

ሚያዚያ ፲፱ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ ቤሕአልድ አዲስአበባ ኢትዮጵያ እስከ ምድር ዳርቻ ምስክሮች ሊሆኑ ለተጠሩት ለቅዱሳን ሐዋርያት በመጀመሪያ የታወጀው አዋጅ የማይሻር፣ ለዘለዓለም ጸንቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ ያለና ሲተላለፍ የሚኖር ሕያው ቃል በመሆኑ ብርሃናተ ዓለም ሐዋርያት፣ ሰባ ሁለቱ አርድዕት የስብከታቸውን ማዕከል ክርስቶስንና የአዳኝነቱን ሥራ በማድረግ አስዋከ ረሲዓንን እየነቀሉ፣ የወንጌልን ምርጥ ዘር በምዕመናን የልቡና ማሳ ላይ እየዘሩ […]

በበርካቶች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ድረ-ገጽ አገልግሎት ጀመረ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለዘመናት በመኳንንት፣ በወይዛይርትና በግለሰቦች አማካኝነት በውርስ፣ በኑዛዜና በስጦታ መልክ የተሰጧትንና በይዞታ አስከብራ ያቆየቻቸውን ቤቶች፣ ሕንፃዎችና ይዞታዎች ረጅም ዘመናት በድርጅቱ ባሳለፉ ቅን የድርጅቱ ሠራተኞች አእምሮ ከመያዝ ባሻገር የሚመለከታቸው ሁሉ እንዲያውቁት በሚስችል መልኩ ተሰንዶ አለመቀመጡ ድርጅቱ በሥሩ የሚገኙ ደንበኞችን በአግባቡ ለማስተዳደር የሚቸገር ከመሆኑም በላይ የሚባክኑ ይዞታዎች መኖራቸውን ይነገራል ። ይህንን የተረዱት የድርጅቱ ዋና […]

ኋላ ቀር የገንዘብ አስተዳደርን በማዘመን የደንበኞችን ውጣ ውረድ የማስቀረት ዓላማን ያነገበው የሞባይል ባንኪንግ አገልግልግሎት በይፋ ተመርቆ ተግባራዊ ተደረገ

የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን የደንበኛ ተኮር አስተዳደር ስርዓት አካል የሆነው የዘመናዊ ገንዘብ አስተዳደር ቴክኖሎጂ ማበልጸግ ተግባራዊ ለማድረግ ከበርካታ ባንኮች ፣ ድርጅቶችና ኤጀንትቶች አማራጭ መንገዶችን ለማየት ተደጋጋሚ ውይይቶችን ማድረጉን መዘጋባችን የሚታወስ ነው። የቀረቡት አማራጮች ሙሉ በሚባል ደረጃ የሚያጓጉ ቢሆኑም ድርጅቱ ጥበብ በተሞላው ምርጫ በመምረጥ ከዐባይ ባንክ አክስዮን ማኅበር አራት ኪሎ ቅርንጫፍ ጋር ለመሥራት […]

የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን ደንበኛ ተኮር ስርዓት ተፈጻሚ ለማድርግ የመጀመሪያውን ምዕራፍ አጠናቆ በዛሬው እለት በይፋ አስመረቀ

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ በሚመሩበት በሳልና አባታዊ የአመራር ጥበብ ካደረጉት ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት ሥራ አካል የሆነው የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በሚፈለገው ልክ ራሱ እየለወጠ ነው። ድርጅቱ ጥር 15 ቀን 1990 ዓ.ም አሁን […]

ላለፉት አራት ቀናት በኬንያ ንይሮቢ በሐዋርያዊ አገልግሎት ላይ የሰነበቱት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል

በኬንያ ናይሮቢ ሐዋርያዊ አገልግሎት ሲያከናውኑ የሰነበቱ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ አመሻሹ ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል። ሁለቱ ብፁዓን አባቶች ሚያዚያ 9ቀን 2018 ዓ.ም ናይሮቢ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የናይሮቢ […]

በፌስቡክ ያግኙን

የመገኛ መረጃዎች

© በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳዯርና ልማት ድርጅት | Website by atbiya.com